ኻሙዲ
==
ኻሙዲ | |
---|---|
ምናልባት ኻሙዲ የሚል ማኅተም? | |
የግብጽ (ሂክሶስ) ፈርዖን | |
ግዛት | 1560-1548 ዓክልበ. ግ. |
ቀዳሚ | አፐፒ |
ተከታይ | (1 አሕሞስ) |
ሥርወ-መንግሥት | 15ኛው ሥርወ መንግሥት |
==
ኻሙዲ በጥንታዊ ግብጽ በ2ኛው ጨለማ ዘመን የ15ኛው ሥርወ መንግሥት (ሂክሶስ) ፈርዖን ነበር።
ስሙ ከቶሪኖ ከፈን ፈርዖኖች ዝርዝርና በኢያሪኮ (ከነዓን ወይም እስራኤል) ከተገኙ ፪ ጥንዚዞች ታውቋል። እንዲሁም ምናልባት ከጌባል ፊንቄ የወጣ ማኅተም በአንዳንድ መምህር ዘንድ «ኻሙዲ» ይላል፣ ሌሎች ግን «ኻንዲ» እንደሚል ይመስላቸዋል።
የራይንድ ሥነ ቁጥራዊ ፓፒሩስ የተባለው ሰነድ ከአፐፒ ዘመን በኋላ በሚከተለው ፈርዖን 11ኛው ዓመት «የደቡብ ንጉሥ» (1 አሕሞስ) ወርሮ ወደ አቫሪስ እንደ ቀረበ ያመልክታል። አሁን ይህ የኻሙዲ 11ኛው ዓመት ማለት እንደ ነበር፣ አቫሪስም ከዚያ ቶሎ እንደ ወደቀ ይታስባል። አቫሪስ ከወደቀ በኋላ ሂክሶስ (አሞራውያን ወገን ሁነው) በዕብራውያን ነገደ ስምዖን ርስት ወደ ነበረው ወደ ሻሩሄን ሸሽተው አሕሞስ በዚያ ለ፫ ዓመት ያህል እንደ ከበባቸው ይታወቃል።
ቀዳሚው አፐፒ | የግብፅ (ሂክሶስ) ፈርዖን 1560-1548 ዓክልበ. ግድም | ተከታይ (1 አሕሞስ) |
🔥 Top keywords: ዋናው ገጽልዩ:Searchስዕል:Keristo1.pdfኢትዮጵያሚካኤል2ኛው ዓለማዊ ጦርነትሥርዓተ ነጥቦችፋይዳ መታወቂያሥነ-ፍጥረትአበበ ቢቂላአማርኛዓፄ ቴዎድሮስSpecial:Searchእርዳታ:ይዞታገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞችውክፔዲያጥላሁን ገሠሠቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴኤችአይቪልዩ:RecentChangesየአድዋ ጦርነትግራኝ አህመድኃይሌ ገብረ ሥላሴሀዲስ ዓለማየሁየቅድስት ድንግል ማርያም ስሞችመጽሐፍ ቅዱስሥላሴየዋና ከተማዎች ዝርዝርአፋር (ክልል)የቃል ክፍሎችበዓሉ ግርማኢየሱስቅዱስ ጊዮርጊስ (ሰማዕት)አዲስ አበባቅዱስ ያሬድትግራይ ክልልእስራኤልየኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠርየኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን